ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘኁልቍ 1:6-21 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

6. ከስምዖን የሱሪሰዳይ ልጅ ሰለሚኤል፤

7. ከይሁዳ የአሚናዳብ ልጅ ነአሶን፤

8. ከይሳኮር የሶገር ልጅ ናትናኤል፤

9. ከዛብሎን የኬሎን ልጅ ኤልያብ፤

10. ከዮሴፍ ልጆች ከኤፍሬም የዓሚሁድ ልጅ ኤሊሳማ፤ከምናሴ የፍዳሱር ልጅ ገማልኤል

11. ከብንያም የጋዴዮን ልጅ አቢዳን፤

12. ከዳን የአሚሳዳይ ልጅ አኪዔዘር፤

13. ከአሴር የኤክራን ልጅ ፋግኤል፤

14. ከጋድ የራጉኤል ልጅ ኤሊሳፍ፤

15. ከንፍታሌም የዔናን ልጅ አኪሬ።”

16. እነዚህ ከማኅበረ ሰቡ የተመረጡ የየነገዱ አለቆች ሲሆኑ እነርሱም የእስራኤል ጐሣዎች መሪዎች ነበሩ።

17. ሙሴና አሮን ስማቸው የተጠቀሰውን እነዚህን ሰዎች ወሰዱ፤

18. ከዚያም በሁለተኛው ወር በመጀመሪያው ቀን ማኅበረ ሰቡን በሙሉ በአንድነት ሰበሰቧቸው። የተሰበሰቡትም በየጐሣቸውና በየቤተ ሰባቸው የትውልድ ሐረጋቸውን ተናገሩ፤

19. እግዚአብሔር ሙሴን ባዘዘው መሠረት ዕድሜአቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ የሆነ ወንዶች ስማቸው አንድ በአንድ ተመዘገበ። እንዲህ አድርጎም በሲና ምድረ በዳ ቈጠራቸው።

20. ከእስራኤል የበኵር ልጅ ከሮቤል ዝርያ ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያ በላይ ሆኖ በሰራዊቱ ውስጥ ለማገልገል ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ።

21. ከሮቤል ነገድ የተቈጠሩት አርባ ስድስት ሺህ አምስት መቶ ነበሩ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘኁልቍ 1