ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘኁልቍ 1:33-39 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

33. ከኤፍሬም ነገድ የተቈጠሩትም አርባ ሺህ አምስት መቶ ነበሩ።

34. ከምናሴ ዝርያዎች፦ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ።

35. ከምናሴ ነገድ የተቈጠሩትም ሠላሳ ሁለት ሺህ ሁለት መቶ ነበሩ።

36. ከብንያም ዝርያ፦ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ፤

37. ከብንያም ነገድ የተቈጠሩትም ሠላሳ አምስት ሺህ አራት መቶ ነበሩ።

38. ከዳን ዝርያ፦ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ።

39. ከዳን ነገድ የተቈጠሩትም ሥልሳ ሁለት ሺህ ሰባት መቶ ነበሩ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘኁልቍ 1