ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዕንባቆም 2:12-19 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

12. “ከተማን ደም በማፍሰስ ለሚሠራ፣በወንጀልም ለሚመሠርታት ወዮለት።

13. ሰዎች ለእሳት ማገዶ እንዲሆን እንዲለፉ፣ሕዝቦችም በከንቱ እንዲደክሙ፣ እግዚአብሔር ጸባኦት ወስኖ የለምን?

14. ውሃ ባሕርን እንደሚሸፍን ሁሉ፣ምድርም የእግዚአብሔርን ክብር በማወቅ ትሞላለችና።

15. “ኀፍረተ ሥጋቸውን ለማየት፤ባልንጀሮቹን ለሚያጠጣ፣እስኪሰክሩም ድረስ ወይን ለሚቀዳላቸው ወዮለት!

16. በክብር ፈንታ ዕፍረት ትሞላለህ፤አሁን ደግሞ ተራው የአንተ ነውና፤ ጠጣ፤ ኀፍረተ ሥጋህም ይገለጥ፤ በእግዚአብሔር ቀኝ እጅ ያለው ጽዋ ይመለስብሃል፤ክብርህንም ውርደት ይሸፍነዋል።

17. በሊባኖስ ላይ የሠራኸው ግፍ ያጥለቀልቅሃል፤እንስሳቱን ማጥፋትህም ያስደነግጥሃል፤የሰው ደም አፍሰሃልና፤አገሮችንና ከተሞችን በውስጣቸው የሚኖሩትንም ሁሉ አጥፍተሃልና።

18. “የሰው እጅ የቀረጸው ጣዖት፣ሐሰትንም የሚናገር ምስል ምን ፋይዳ አለው?ሠሪው በገዛ እጁ ሥራ ይታመናልና፣መናገር የማይችሉ ጣዖታትን ይሠራልና።

19. ዕንጨቱን፣ ‘ንቃ!’ሕይወት የሌለውንም ድንጋይ፣ ‘ተነሣ!’ ለሚል ወዮለት፤በውኑ ማስተማር ይችላልን?እነሆ፤ በወርቅና በብር ተለብጦአል፤እስትንፋስም የለውም።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዕንባቆም 2