ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤርምያስ 51:37-51 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

37. ባቢሎን የፍርስራሽ ክምር፣የቀበሮዎች መፈንጫ፣የድንጋጤና የመሣለቂያ ምልክት ትሆናለች፤የሚኖርባትም አይገኝም።

38. ሕዝቦቿ ሁሉ እንደ ደቦል አንበሳ ያገሣሉ፤እንደ አንበሳ ግልገልም ያጒረመርማሉ።ጒሮሮአቸው በደረቀ ጊዜድግስ አዘጋጅላቸዋለሁ፤እንዲሰክሩም አደርጋቸውና፤”

39. በሣቅ እየፈነደቁ፣ለዘላለም ላይነቁ ይተኛሉ።”ይላል እግዚአብሔር።

40. “እንደ ጠቦት፣እንደ አውራ በግና እንደ ፍየል፣ወደ መታረድ አወርዳቸዋለሁ።

41. “ሼሻክ እንዴት ተማረከች!የምድር ሁሉ ትምክህትስ እንዴት ተያዘች!ባቢሎን በሕዝብ ሁሉ ዘንድ፣ምንኛ አስደንጋጭ ሆነች።

42. ባሕር በባቢሎን ላይ ይወጣል፤ሞገዱም እየተመመ ይሸፍናታል።

43. ከተሞቿ ሰው የማይኖርባቸው፣ዝርም የማይልባቸው፣ደረቅና በረሓማ ቦታ፣ባድማ ምድርም ይሆናሉ።

44. ቤልን በባቢሎን ውስጥ እቀጣለሁ፤የዋጠውን አስተፋዋለሁ፤ሕዝቦች ከእንግዲህ ወደ እርሱ አይጐርፉም፤የባቢሎንም ቅጥር ይወድቃል።

45. “ሕዝቤ ሆይ፤ ከመካከሏ ውጡሕይወታችሁን አትርፉ!ከአስፈሪው የእግዚአብሔር ቍጣ አምልጡ።

46. ወሬ በምድሪቱ ሲሰማ፣ተስፋ አትቍረጡ፤ አትፍሩም፤ገዥ በገዥ ላይ ስለ መነሣቱ፣ዐመፅም በምድሪቱ ስለ መኖሩ፣አንድ ወሬ ዘንድሮ፣ ሌላውም ለከርሞ ይመጣል፤

47. የባቢሎንን ጣዖታት የምቀጣበት ጊዜ፣በርግጥ ይመጣልና።ምድሯ በሙሉ ትዋረዳለች፤የታረዱትም በሙሉ በውስጧ ይወድቃሉ።

48. ሰማይና ምድር በውስጣቸውም ያለው ሁሉ፣በባቢሎን ላይ እልል ይላሉ፤አጥፊዎች ከሰሜን ወጥተው፣እርሷን ይወጓታልና፤”ይላል እግዚአብሔር።

49. “በምድር ሁሉ የታረዱት፣በባቢሎን ምክንያት እንደ ወደቁ፣ባቢሎንም በእስራኤል በታረዱት ምክንያት መውደቅ ይገባታል።

50. ከሰይፍ ያመለጣችሁ ሆይ፤ሂዱ! ጊዜ አትፍጁ፤በሩቅ ምድር ያላችሁ እግዚአብሔርን አስታውሱ፤ኢየሩሳሌምንም አስቧት።”

51. “ባዕዳን ሰዎች ወደ ተቀደሰው፣ወደ እግዚአብሔር ቤት ስለ ገቡ፣እኛ ተሰድበናል፤ዕፍረትም ፊታችንን ሸፍኖአል፤ውርደትም ተከናንበናል።”

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኤርምያስ 51