ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤርምያስ 51:31-40 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

31. ከተማዪቱ ሙሉ በሙሉ መያዟን፣ለባቢሎን ንጉሥ ለመንገር፣አንዱ ወሬኛ ሌላውን ወሬኛ፣አንዱ መልእክተኛ ሌላውን መልእክተኛ ወዲያው ወዲያው ይከተላል፤

32. መልካዎቿ እንደተያዙ፣የወንዝ ዳር ምሽጎቿ እንደ ተቃጠሉ፣ወታደሮቿም እንደ ተደናገጡ ሊነግሩት ይሯሯጣሉ።”

33. የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“የባቢሎን ሴት ልጅ በመረገጥ ላይ እንዳለ፣የእህል መውቂያ አውድማ ናት፤የመከር ወራቷም ፈጥኖ ይደርስባታል።

34. “የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር በላን፣አድቅቆ ፈጨን፤እንደ ባዶ ማድጋ አደረገን፤እንደ ዘንዶ ዋጠን፣እንደ ጣፋጭ በልቶን ሆዱን ሞላ፤በኋላም አንቅሮ ተፋን፤

35. የጽዮን ነዋሪዎች፣ እንዲህ ይላሉ፤“በሥጋችን ላይ የተፈጸመው ግፍ በባቢሎን ላይ ይሁን፤”ኢየሩሳሌም እንዲህ ትላለች፤“ደማችን በባቢሎን ምድር በሚኖሩት ላይ ይሁን።”

36. ስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“እነሆ፤ እሟገትልሻለሁ፣በቀልሽንም እኔ እበቀልልሻለሁ፤ባሕሯን አደርቃለሁ፣የምንጮቿንም ውሃ።

37. ባቢሎን የፍርስራሽ ክምር፣የቀበሮዎች መፈንጫ፣የድንጋጤና የመሣለቂያ ምልክት ትሆናለች፤የሚኖርባትም አይገኝም።

38. ሕዝቦቿ ሁሉ እንደ ደቦል አንበሳ ያገሣሉ፤እንደ አንበሳ ግልገልም ያጒረመርማሉ።ጒሮሮአቸው በደረቀ ጊዜድግስ አዘጋጅላቸዋለሁ፤እንዲሰክሩም አደርጋቸውና፤”

39. በሣቅ እየፈነደቁ፣ለዘላለም ላይነቁ ይተኛሉ።”ይላል እግዚአብሔር።

40. “እንደ ጠቦት፣እንደ አውራ በግና እንደ ፍየል፣ወደ መታረድ አወርዳቸዋለሁ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኤርምያስ 51