ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤርምያስ 48:43-47 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

43. የሞዓብ ሕዝብ ሆይ፤ሽብርና ጒድጓድ፣ ወጥመድም ይጠብቅሃል፤”ይላል እግዚአብሔር።

44. “ከሽብር የሚሸሽ ሁሉ፣ጒድጓድ ውስጥ ይገባል፤ከጒድጓዱም የሚወጣ፣በወጥመድ ይያዛል፤በሞዓብ ላይ፣የቅጣቱን ዓመት አመጣለሁና፣”ይላል እግዚአብሔር፤

45. “የሞዓብን ግንባር፣የደንፊዎችን ዐናት የሚያቃጥል፣እሳት ከሐሴቦን፣ነበልባል ከሴዎን ቤት ወጥቶአልና፤ኰብላዮች በሐሴቦን ጥላ ሥር፣ተስፋ ቈርጠው ቆመዋል።

46. ሞዓብ ሆይ፤ ወዮልህ!የካሞሽ ሕዝብ ተደምስሶአል፤ወንዶች ልጆችህ በምርኮ ተወስደዋል፤ሴቶች ልጆችህም ተግዘዋል።

47. “ነገር ግን የኋላ ኋላ፣የሞዓብን ምርኮ እመልሳለሁ፤”ይላል እግዚአብሔር።በሞዓብ ላይ የተወሰነው ፍርድ ይኸው ነው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኤርምያስ 48