ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤርምያስ 33:16-20 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

16. በዚያ ዘመን ይሁዳ ይድናል፤ኢየሩሳሌም በሰላም ትኖራለች፤የምትጠራበትም ስም፣“እግዚአብሔር ጽድቃችን” የሚል ይሆናል።’

17. እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፤ ‘ከዳዊት ዘር በእስራኤል ቤት ዙፋን ላይ የሚቀመጥ ሰው ፈጽሞ አይታጣም፤

18. ሌዋውያን ከሆኑት ካህናትም የሚቃጠል መሥዋዕት ለማቅረብ፣ የእህል ቍርባን ለማቃጠልና ሌላውንም መሥዋዕት ለመሠዋት ሁል ጊዜ በፊቴ የሚቆም ሰው አይታጣም።’ ”

19. የእግዚአብሔር ቃል ወደ ኤርምያስ እንዲህ ሲል መጣ፤

20. “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ለቀንና ለሌሊት የወሰንሁትን ሥርዐት በማፋለስ ቀንና ሌሊት በተወሰነላቸው ጊዜ እንዳይፈራረቁ ኪዳኔን ማፍረስ ብትችሉ፣

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኤርምያስ 33