20. ልጆቻቸው እንደ ቀድሞው ይሆናሉ፤ማኅበረ ሰቡም በፊቴ የጸና ይሆናል፤የሚጨቍኗቸውን ሁሉ እቀጣለሁ።
21. መሪያቸው ከራሳቸው ወገን ይሆናል፤ገዣቸውም ከመካከላቸው ይነሣል፤ወደ እኔ አቀርበዋለሁ፤ እርሱም ይቀርበኛል፤አለዚያማ ደፍሮ፣ወደ እኔ የሚቀርብ ማን ነው?ይላል እግዚአብሔር።
22. “ ‘ስለዚህ እናንተ ሕዝብ ትሆኑኛላችሁ፤እኔም አምላክ እሆናችኋለሁ።’ ”
23. እነሆ፣ የእግዚአብሔር ማዕበል፣በቍጣ ይነሣል፤የሚገለባብጥም ዐውሎ ነፋስ፣በክፉዎች ዐናት ላይ ይወርዳል።
24. የልቡን ሐሳብ ሳይፈጽም፣ የእግዚአብሔር ቍጣ፣እንዲሁ አይመለስም፤በሚመጡትም ዘመናት፣ይህን ታስተውላላችሁ።