ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤርምያስ 3:1-4 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. “ሰው ሚስቱን ቢፈታ፣እርሷም ሄዳ ሌላ ሰው ብታገባ፣ወደ እርሷ ይመለሳልን?ምድሪቱስ ፈጽማ አትረክስምን?አንቺ ግን ከብዙ ወዳጆችሽ ጋር አመንዝረሻል፤ታዲያ አሁን ወደ እኔ መመለስ ትፈልጊያለሽን?”ይላል እግዚአብሔር።

2. “እስቲ ቀና ብለሽ ጭር ያሉትን ኰረብቶች ተመልከቺ፣በርኵሰት ያልተጋደምሽበት ቦታ ይገኛልን?በበረሓ፣ እንደ ተቀመጠ ዘላን ዐረብ፣በየመንገዱ ዳር ተቀምጠሽ ወዳጆችሽን ጠበቅሽ።በዝሙትሽና በክፋትሽ፣ምድሪቱን አረከስሽ።

3. ስለዚህ ካፊያ ተከለከለ፤ኋለኛው ዝናብም ጠፋ።አንቺ ግን አሁንም የጋለሞታ ገጽታ አለብሽ፤ዐይንሽን በዕፍረት አልሰብር ብለሻል።

4. አሁንም ወደ እኔ ተጣርተሽ፣‘አባቴ፣ የልጅነት ወዳጄ፣

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኤርምያስ 3