15. “ወንድ ልጅ ተወልዶልሃል” ብሎ፣ለአባቴ የምሥራች የነገረ፣ደስ ያሰኘውም ሰው የተረገመ ይሁን።
16. ያ ሰው እግዚአብሔር ሳይራራ፣እንደ ገለበጣቸው ከተሞች ይሁን፤በማለዳ ዋይታን፣በቀትርም የጦርነትን ውካታ ይስማ፤
17. እናቴ መቃብር ትሆነኝ ዘንድ፣ማሕፀንም ሰፊ የዘላለም ማደሪያዬ እንዲሆን፣ከማሕፀንም ሳልወጣ አልገደለኝምና።
18. ችግርና ሐዘንን ለማየት፣ዘመኔንም በውርደት ለመፈጸም፣ለምን ከማሕፀን ወጣሁ?