ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤርምያስ 20:13-18 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

13. ለእግዚአብሔር ዘምሩ፤ ለእግዚአብሔር ምስጋናን አቅርቡ፤የችግረኛውን ነፍስ፣ከክፉዎች እጅ ታድጎአልና።

14. የተወለድሁባት ዕለት የተረገመች ትሁን፤እናቴ እኔን የወለደችባት ቀን አትባረክ።

15. “ወንድ ልጅ ተወልዶልሃል” ብሎ፣ለአባቴ የምሥራች የነገረ፣ደስ ያሰኘውም ሰው የተረገመ ይሁን።

16. ያ ሰው እግዚአብሔር ሳይራራ፣እንደ ገለበጣቸው ከተሞች ይሁን፤በማለዳ ዋይታን፣በቀትርም የጦርነትን ውካታ ይስማ፤

17. እናቴ መቃብር ትሆነኝ ዘንድ፣ማሕፀንም ሰፊ የዘላለም ማደሪያዬ እንዲሆን፣ከማሕፀንም ሳልወጣ አልገደለኝምና።

18. ችግርና ሐዘንን ለማየት፣ዘመኔንም በውርደት ለመፈጸም፣ለምን ከማሕፀን ወጣሁ?

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኤርምያስ 20