ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤርምያስ 2:12-19 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

12. ሰማያት ሆይ፤ በዚህ ተገረሙ፤በታላቅ ድንጋጤም ተንቀጥቀጡ፤”ይላል እግዚአብሔር።

13. “ሕዝቤ ሁለት ኀጢአት ፈጽመዋል፣ሕያው የውሃ ምንጭ የሆንሁትን፣እኔን ትተዋል፤ውሃ መያዝ የማይችሉትን ቀዳዳ የውሃ ማጠራቀሚያ ጉድጓዶች፣ለራሳቸው ቈፍረዋል።

14. እስራኤል ባሪያ ነውን? ወይስ የቤት ውልድ ባሪያ?ታዲያ፣ ስለ ምን ለብዝበዛ ተዳረገ?

15. አንበሶች በእርሱ ላይ አገሡ፤በኀይለኛ ድምፅም ጮኹበት።ምድሩን ባድማ አድርገውበታል፤ከተሞቹ ተቃጥለዋል፤ ወናም ሆነዋል።

16. ደግሞም የሜምፎስና የጣፍናስ ሰዎች፣መኻል ዐናትሽን ላጩሽ።

17. በመንገድ የሚመራሽን፣ እግዚአብሔር አምላክሽን በመተውሽ፣ይህን በራስሽ ላይ አላመጣሽምን?

18. ከሺሖር ወንዝ ውሃ ለመጠጣት፣አሁንስ ለምን ወደ ግብፅ ወረድሽ?ከኤፍራጥስ ወንዝስ ውሃ ለመጠጣት፣ወደ አሦር መውረድ ለምን አስፈለገሽ?

19. ክፋትሽ ቅጣት ያስከትልብሻል፤ክህደትሽም ተግሣጽ ያመጣብሻል፤ እግዚአብሔር አምላክሽን ስትተዪ፣እኔንም መፍራት ችላ ስትይ፣ምን ያህል ክፉና መራራ እንደሚሆንብሽ፣አስቢ፤ እስቲ አስተውዪ፤”ይላል የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኤርምያስ 2