ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤርምያስ 12:3-13 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

3. ነገር ግን እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ እኔን ታውቀኛለህ፤ ታየኛለህ፤ስለ አንተም ያለኝን ሐሳብ ትመረምራለህ።እንደሚታረዱ በጎች ንዳቸው፤ለዕርድም ቀን ለይተህ አቈያቸው፤

4. ምድሪቱ በዝናብ እጦት የምትጐዳው፣የሜዳውም ሣር ሁሉ በድርቅ የሚመታው እስከ መቼ ነው?ከነዋሪዎቿ ክፋት የተነሣ፣እንስሳትና አዕዋፍ ጠፍተዋል፤ደግሞም ሕዝቡ፣“በእኛ ላይ የሚሆነውን አያይም” ብለዋል።

5. “ከእግረኞች ጋር ሮጠህ፣እነርሱ ካደከሙህ፣ከፈረሰኞች ጋር እንዴት ልትወዳደር ትችላለህ?በሰላም አገር ከተሰናከልህ፣በዮርዳኖስ ደን ውስጥ እንዴት ልትሆን ነው?

6. ወንድሞችህና የገዛ ቤተ ሰብህ፣እነርሱ እንኳ አሢረውብሃል፣በአንተም ላይ ይጮኻሉ፤በመልካም ቢናገሩህም እንኳአትመናቸው።

7. “ቤቴን እተዋለሁ፤ርስቴን እጥላለሁ፤የምወዳትን እርሷን፣አሳልፌ በጠላቶቿ እጅ እሰጣታለሁ።

8. ርስቴ፣ በዱር እንዳለ አንበሳተነሥታብኛለችበእኔም ላይ ጮኻብኛለች፤ስለዚህ ጠላኋት።

9. ርስቴ ሌሎች አሞሮች፣ሊበሏት እንደ ከበቧት፣እንደ ዝንጒርጒር አሞራ አልሆነችምን?ሂዱ፤ የዱር አራዊትን ሁሉ ሰብስቡ፤እንዲቀራመቷትም አምጧቸው።

10. ብዙ እረኞች የወይን ቦታዬን ያጠፋሉ፤ይዞታዬንም ይረግጣሉ፤ደስ የምሰኝበትንም ማሳ፣ጭር ያለ በረሓ ያደርጉታል።

11. በፊቴ ባድማ፣ደረቅና ወና ይሆናል፤መላዪቱም ምድር ጠፍ ትሆናለች፤ስለ እርሷ የሚገደው የለምና።

12. በምድረ በዳ ባሉት ወና ኰረብቶች ላይ፣አጥፊዎች ይሰማራሉ፤ የእግዚአብሔር ሰይፍ ከምድር ጫፍ እስከ ምድር ጫፍ፣አንዳች ሳያስቀር ይበላል፤የሚተርፍም የለም።

13. ስንዴን ይዘራሉ፤ እሾኽን ያጭዳሉ፤ይደክማሉ፤ የሚያገኙት ግን የለም፤ ከእግዚአብሔርም ጽኑ ቍጣ የተነሣ፣በመኸራችሁ ውጤት ታፍራላችሁ።”

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኤርምያስ 12