ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 8:7-16 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

7. ጅማሬህ አነስተኛ ቢመስልም፣ፍጻሜህ እጅግ ታላቅ ይሆናል።

8. “የቀደመውን ትውልድ ጠይቅ፤አባቶቻቸውም የደረሱበትን መርምረህ አግኝ፤

9. እኛ ትናንት ስለ ተወለድን አንዳች አናውቅምና፤ዘመናችንም በምድር ላይ እንደ ጥላ ነው።

10. እነርሱ የሚያስተምሩህና የሚነግሩህ፣ከልቦናቸውም ቃልን የሚያወጡ አይደሉምን?

11. ደንገል ረግረግ በሌለበት ስፍራ ይበቅላልን?ቄጠማስ ውሃ በሌለበት ይለመልማልን?

12. ገና በማደግ ላይ እያለ ሳይታጨድ፣ከሌሎች ዕፀዋት ፈጥኖ ይደርቃል።

13. እግዚአብሔርን የሚረሱ መጨረሻቸው እንዲህ ነው፤አምላክ የለሽ ኑሮ የሚኖሩም ሁሉ ተስፋቸው ትጠፋለች።

14. መተማመኛው ቀጭን ክር፣ድጋፉም የሸረሪት ድር ነው።

15. ድሩ ላይ ቢደገፍ፣ ይበጠስበታል፤አጥብቆም ቢይዘው አይጸናም።

16. ውሃ እንደ ጠገበ ተክል፣ ፀሓይ እየሞቀው፣ቅርንጫፉን ሁሉ በአትክልቱ ስፍራ ላይ ይዘረጋል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 8