ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 8:1-8 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ሹሐዊውም በልዳዶስ እንዲህ ሲል መለሰ፤

2. “እንዲህ ያለውን ነገር የምትናገረው፣ቃልህም እንደ ብርቱ ነፋስ የሚሆነው እስከ መቼ ነው?

3. እግዚአብሔር ፍትሕን ያጣምማልን?ሁሉን ቻይ አምላክስ ጽድቅን ያጣምማልን?

4. ልጆችህ በእርሱ ላይ ኀጢአት ሠርተው ከሆነ፣ለኀጢአታቸው ቅጣት አሳልፎ ሰጥቶአቸዋል።

5. ነገር ግን አንተ ወደ እግዚአብሔር ብትመለከት፣ሁሉን ቻይ አምላክን ብትማፀን፣

6. ንጹሕና ቅን ብትሆን፣ እርሱ ስለ አንተ አሁኑኑ ይነሣል፤ወደ ተገቢውም ስፍራህ ይመልስሃል።

7. ጅማሬህ አነስተኛ ቢመስልም፣ፍጻሜህ እጅግ ታላቅ ይሆናል።

8. “የቀደመውን ትውልድ ጠይቅ፤አባቶቻቸውም የደረሱበትን መርምረህ አግኝ፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 8