ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 7:8-18 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

8. አሁን የሚያየኝ ሰው ዐይን ከእንግዲህ አያየኝም፤ትፈልገኛለህ፤ እኔ ግን የለሁም።

9. ደመና በኖ እንደሚጠፋ፣ወደ መቃብር የሚወርድም አይመለስም።

10. ወደ ቤቱ ዳግመኛ አይመለስም፤ስፍራውም ከእንግዲህ አያውቀውም።

11. “ስለዚህ ከቶ ዝም አልልም፤በመንፈሴ ጭንቀት እናገራለሁ፤በነፍሴም ምሬት አጒረመርማለሁ።

12. በላዬ ጠባቂ ታደርግ ዘንድ፣እኔ ባሕር ነኝን ወይስ የባሕር አውሬ?

13. አልጋዬ ያጽናናኛል፣መኝታዬም ማጒረምረሜን ይቀንስልኛል ባልሁ ጊዜ፣

14. አንተ በሕልም ታስፈራራኛለህ፤በራእይም ታስደነግጠኛለህ፤

15. ስለዚህ እንዲህ ሆኖ ከመኖር፣መታነቅና መሞትን እመርጣለሁ።

16. ሕይወቴን እጸየፋለሁ፤ ዘላለም መኖር አልፈልግም፣ዘመኔ እንደ እስትንፋስ ነውና ተወኝ።

17. “ከፍ ከፍ ታደርገው ዘንድ፣ልብህንም ትጥልበት ዘንድ ሰው ምንድን ነው?

18. በየማለዳው ትመረምረዋለህ፤በየጊዜውም ትፈትነዋለህ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 7