ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 6:8-21 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

8. “ምነው ልመናዬ በተመለሰልኝ፤እግዚአብሔር የምመኘውን በሰጠኝ፤

9. እግዚአብሔር አድቅቆ ያጠፋኝ ዘንድ፣ምነው እጁ በተፈታ!

10. ፋታ በማይሰጥ ሕመም ውስጥ እየተደሰትሁ፣ይህ መጽናኛ በሆነልኝ ነበር፤የቅዱሱን ትእዛዝ አልጣስሁምና።

11. “አሁንም ተስፋ አደርግ ዘንድ ብርታቴ፣እታገሥስ ዘንድ አለኝታዬ ምንድን ነው?

12. የድንጋይ ጒልበት አለኝን?ሥጋዬስ ናስ ነውን?

13. ያልተሳካልኝ ሰው ነኝና፣ራሴን ለመርዳት ምን ጒልበት አለኝ?

14. “ለወዳጁ በጎነት የማያሳይ ሰው፣ሁሉን የሚችለውን አምላክ መፍራት ትቶአል።

15. ወንድሞቼ ግን እንደማያዛልቅ ጅረት፣ለጊዜው ሞልቶ እንደሚፈስ ወንዝ የማይታመኑ ናቸው፤

16. በረዶ በሟሟ ጊዜ ወንዙ ይደፈርሳል፤ዐመዳይም በቀለጠ ጊዜ ይሞላል፤

17. በበጋ ወራት ግን ይጠፋል፤በሙቀትም ጊዜ መፋሰሻው ላይ አይገኝም።

18. ሲራራ ነጋዴዎች ውሃ አጥተው መንገዳቸውን ይቀይራሉ፤ወደ በረሓም ገብተው ይጠፋሉ።

19. የቴማን ነጋዴዎች ውሃ ይፈልጋሉየሳባ መንገደኞችም ተስፋ ያደርጋሉ፤

20. እርግጠኞች ሆነው ስለ ነበር ተሰቀቁ፤እዚያ ደረሱ፣ ግን ዐፈሩ።

21. አሁንም እናንተ እንደዚያ ሆናችሁብኝ፣መከራዬን አይታችሁ ፈራችሁ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 6