ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 5:9-21 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

9. እርሱ፣ የማይመረመሩ ድንቅ ነገሮች፣የማይቈጠሩም ታምራት ያደርጋል።

10. ምድሪቱን በዝናብ ያረሰርሳል፤ሜዳውንም ውሃ ያጠጣል።

11. የተዋረዱትን በከፍታ ቦታ ያስቀምጣል፤ያዘኑትንም ወደ አስተማማኝ ስፍራ ያወጣቸዋል።

12. እጃቸው ያሰቡትን እንዳይፈጽም፣የተንኰለኞችን ዕቅድ ያከሽፋል።

13. ጠቢባንን በጥበባቸው ይይዛል፤የተንኰለኞችንም ሤራ ያጠፋል።

14. ቀኑ ጨለማ ይሆንባቸዋል፤በቀትርም ጊዜ በሌሊት እንዳለ ሰው በዳበሳ ይሄዳሉ።

15. ችግረኛውን ከአፋቸው ሰይፍ፣ከኀይለኛውም እጅ ያድነዋል።

16. ስለዚህ ድኻ ተስፋ አለው፤ዐመፅም አፏን ትዘጋለች።

17. “እነሆ፤ እግዚአብሔር የሚገሥጸው ሰው ምስጉን ነው፤ስለዚህ ሁሉን የሚችለውን አምላክ ተግሣጽ አትናቅ።

18. እርሱ ያቈስላል፤ ይፈውሳል፤እርሱ ይሰብራል፤ በእጁም ይጠግናል፤

19. እርሱ ከስድስት መቅሠፍት ይታደግሃል፤በሰባተኛውም ጒዳት አያገኝህም።

20. በራብ ጊዜ ከሞት፣በጦርነትም ከሰይፍ ያድንሃል።

21. ከምላስ ጅራፍ ትሰወራለህ፤ጥፋት ሲመጣም አትፈራም።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 5