ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 5:6-13 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

6. ችግር ከምድር አይፈልቅም፤መከራም ከመሬት አይበቅልም።

7. ፍንጣሪው ከእሳቱ ላይ ሽቅብ እንደሚወረወር፣ሰውም ለመከራ ይወለዳል።

8. “እኔ ብሆን ኖሮ፣ ወደ እግዚአብሔር በቀረብሁ፣ጒዳዬንም በፊቱ በገለጽሁለት ነበር።

9. እርሱ፣ የማይመረመሩ ድንቅ ነገሮች፣የማይቈጠሩም ታምራት ያደርጋል።

10. ምድሪቱን በዝናብ ያረሰርሳል፤ሜዳውንም ውሃ ያጠጣል።

11. የተዋረዱትን በከፍታ ቦታ ያስቀምጣል፤ያዘኑትንም ወደ አስተማማኝ ስፍራ ያወጣቸዋል።

12. እጃቸው ያሰቡትን እንዳይፈጽም፣የተንኰለኞችን ዕቅድ ያከሽፋል።

13. ጠቢባንን በጥበባቸው ይይዛል፤የተንኰለኞችንም ሤራ ያጠፋል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 5