ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 36:3-11 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

3. ዕውቀቴን ከሩቅ አመጣለሁ፤ፈጣሪዬ ጻድቅ እንደሆነ እገልጻለሁ።

4. ቃሌ ሐሰት እንዳልሆነ አረጋግጣለሁ፤በዕውቀቱ ፍጹም የሆነ ሰው ከአንተ ጋር ነው።

5. “እግዚአብሔር ኀያል ነው፤ ግን ማንንም አይንቅም፤ኀያል፣ በዐላማውም ጽኑ ነው።

6. ክፉዎችን በሕይወት አያኖርም፤ለተቸገሩት ግን በቅን ይፈርዳል።

7. ዐይኖቹን ከጻድቃን ላይ አያነሣም፤ከነገሥታት ጋር በዙፋን ላይ ያስቀምጣቸዋል፤ለዘላለምም ከፍ ከፍ ያደርጋቸዋል።

8. ነገር ግን ሰዎች በሰንሰለት ቢታሰሩ፣በመከራም ገመድ ቢጠፈሩ፣

9. በእብሪት የፈጸሙትን በደል፣ተግባራቸውን ይነግራቸዋል።

10. ተግሣጽን እንዲሰሙ ያደርጋቸዋል፤ከክፋታቸውም እንዲመለሱ ያዛቸዋል።

11. ታዘው ቢያገለግሉት፣ቀሪ ዘመናቸውን በተድላ፣ዕድሜያቸውንም በርካታ ይፈጽማሉ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 36