ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 35:4-12 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

4. “ለአንተና አብረውህ ላሉት ባልንጀሮችህ፣መልስ መስጠት እፈልጋለሁ።

5. ቀና ብለህ ወደ ሰማይ እይ፤ከአንተ በላይ ከፍ ብለው ያሉትንም ደመናት ተመልከት።

6. ኀጢአትህስ ቢበዛ እርሱን ምን ትጐዳዋለህ?ኀጢአትህስ ቢበዛ ምን ያደርገዋል?

7. ጻድቅ ብትሆንም ለእርሱ ምን ትሰጠዋለህ?ከእጅህስ ምን ይቀበላል?

8. ክፋትህ የሚጐዳው እንዳንተ ያለውን ሰው ብቻ ነው፤ጽድቅህም የሚጠቅመው የሰውን ልጆች ብቻ ነው።

9. “ሰው ከጭቈና ብዛት የተነሣ ይጮኻል፤ከኀያሉም ክንድ ሥር ለመውጣት ለርዳታ ይጣራል።

10. ነገር ግን እንዲህ የሚል የለም፤ ‘ፈጣሪዬ እግዚአብሔር ወዴት ነው?በሌሊት መዝሙርን የሚሰጥ፣

11. ከምድር እንስሳት ይልቅ የሚያስተምረን፣ከሰማይ ወፎችም ይልቅ ጠቢባን የሚያደርገን፣ እርሱ የት አለ?’

12. ከዐመፀኞች ትዕቢት የተነሣ፣ሰዎች ሲጮኹ አይመልስላቸውም፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 35