ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 35:1-6 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ኤሊሁ ንግግሩን በመቀጠል እንዲህ አለ፤

2. “ ‘በእግዚአብሔር ፊት ንጹሕ ነኝ’ ማለትህ፣ትክክል ይመስልሃልን?

3. ደግሞ ‘ያገኘሁት ጥቅም ምንድን ነው?ኀጢአት ባለ መሥራቴስ ምን አተረፍሁ?’ ብለህ ጠይቀኸዋል።

4. “ለአንተና አብረውህ ላሉት ባልንጀሮችህ፣መልስ መስጠት እፈልጋለሁ።

5. ቀና ብለህ ወደ ሰማይ እይ፤ከአንተ በላይ ከፍ ብለው ያሉትንም ደመናት ተመልከት።

6. ኀጢአትህስ ቢበዛ እርሱን ምን ትጐዳዋለህ?ኀጢአትህስ ቢበዛ ምን ያደርገዋል?

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 35