ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 31:19-28 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

19. በልብስ ዕጦት ሰው ሲጠፋ፣ወይም ዕርቃኑን ያልሸፈነ ድኻ አይቼ፣

20. በበጎቼ ጠጒር ስላሞቅሁት፣ልቡ ባርኮኝ ካልሆነ፣

21. በአደባባይ ተሰሚነት አለኝ ብዬ፣በድኻ አደጉ ላይ እጄን አንሥቼ ከሆነ፣

22. ትከሻዬ ከመጋጠሚያው ይነቀል፤ክንዴም ከመታጠፊያው ይሰበር፤

23. የእግዚአብሔርን ቍጣ በመፍራቴ፣እንዲህ ያሉ ነገሮች መፈጸም አልቻልሁም።

24. “ወርቅን ተስፋ አድርጌ፣ወይም ንጹሑን ወርቅ፣ ‘አንተ መታመኛዬ ነህ’ ብዬ ከሆነ፣

25. እጄ ባገኘችው ሀብት፣በባለጠግነቴም ብዛት ደስ ብሎኝ ከሆነ፣

26. የፀሓይን ድምቀት አይቼ፣ወይም የጨረቃን አካሄድ ግርማ ተመልክቼ፣

27. ልቤ በስውር ተታልሎ፣ስለ ክብራቸው አፌ እጄን ስሞ ከሆነ፣

28. ለልዑል እግዚአብሔር ታማኝ አለመሆኔ ነውና፣ይህም ደግሞ የሚያስቀጣኝ በደል በሆነ ነበር።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 31