ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 31:13-20 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

13. “ወንዶችና ሴቶች አገልጋዮቼ አቤቱታ ባቀረቡ ጊዜ፣ፍርድ አዛብቼ ከሆነ፣

14. እግዚአብሔር ሲነሣ ምን አደርጋለሁ?ሲጠይቀኝስ ምን መልስ እሰጣለሁ?

15. እኔን በማሕፀን ውስጥ የፈጠረኝ እነርሱን የፈጠረ አይደለምን?በሆድ ውስጥ የሠራንስ እርሱ ራሱ አይደለምን?

16. “ለድኻ የሚያስፈልገውን ከልክዬ ከሆነ፣ወይም የመበለቲቱን ዐይን አፍዝዤ ከሆነ፣

17. እንጀራዬን ከድኻ አደጉ ጋር ሳልካፈል፣ለብቻዬ በልቼ ከሆነ፣

18. ይልቁን ድኻ አደጉን ከታናሽነቴ ጀምሮ እንደ አባት አሳደግሁት፤መበለቲቱንም ከተወለድሁ ጀምሮ መንገድ መራኋት፤

19. በልብስ ዕጦት ሰው ሲጠፋ፣ወይም ዕርቃኑን ያልሸፈነ ድኻ አይቼ፣

20. በበጎቼ ጠጒር ስላሞቅሁት፣ልቡ ባርኮኝ ካልሆነ፣

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 31