ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 29:8-17 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

8. ጐበዛዝት አይተውኝ ገለል ይሉ፣ሽማግሌዎችም ተነሥተው ይቆሙ ነበር።

9. የሰፈሩ ታላላቅ ሰዎች ከመናገር ይቈጠቡ፣እጃቸውንም በአፋቸው ላይ ይጭኑ ነበር፤

10. የመኳንንት ድምፅ ጸጥ ይል፣ምላሳቸውም ከላንቃቸው ጋር ይጣበቅ ነበር፤

11. የሰሙኝ ሁሉ ያሞጋግሱኝ፣ያዩኝም ያመሰግኑኝ ነበር፤

12. ለርዳታ የሚጮኸውን ችግረኛ፣ድኻ ዐደጉንም ታድጌአለሁና።

13. በሞት አፋፍ ላይ የነበረ መርቆኛል፤የመበለቲቱንም ልብ አሳርፌአለሁ።

14. ጽድቅን እንደ ልብስ ለበስሁ፤ፍትሕም መጐናጸፊያዬና ጥምጥሜ ነበር።

15. ለዕዉራን ዐይን፣ለአንካሶችም እግር ነበርሁ።

16. ለችግረኛው አባት፣ለባይተዋሩ ተሟጋች ነበርሁ።

17. የኀጢአተኛውን ክራንቻ ሰበርሁ፤የነጠቀውንም ከጥርሶቹ አስጣልሁ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 29