ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 27:5-12 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

5. እናንተን እንደ ቅኖች መቍጠር፣የማላደርገው ነገር ነው፤ ጨዋነቴንም እስክሞት ድረስ አልጥልም።

6. ጽድቄን አጥብቄ እይዛለሁ፤ አልለቀውምም፤በዘመኔም ሁሉ ኅሊናዬ አይወቅሰኝም።

7. “ጠላቴ እንደ በደለኛ፣ባላንጣዬም እንደ ክፉ ይሁን።

8. እግዚአብሔር ሲያስወግደው፣ነፍሱንም ሲወስድበት ዐመፀኛ ምን ተስፋ አለው?

9. በውኑ መከራ በገጠመው ጊዜ፣እግዚአብሔር ጩኸቱን ይሰማልን?

10. ሁሉን በሚችል አምላክ ደስ ይለዋልን?ዘወትርስ እግዚአብሔርን ይጠራልን?

11. “ስለ እግዚአብሔር ክንድ አስተምራችኋለሁ፤የሁሉን ቻዩንም አምላክ ዕቅድ አልሸሽግም።

12. ሁላችሁ ይህን አይታችኋል፤ታዲያ፣ ይህ ከንቱ ንግግር ምንድን ነው?

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 27