ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 23:1-5 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ኢዮብም እንዲህ ሲል መለሰ፤

2. “ዛሬም ሐዘኔ መራራ ነው፤እያቃሰትሁ እንኳ እጁ በላዬ ከብዳለች።

3. እርሱን የት እንደማገኘው ባወቅሁ፤ወደ መኖሪያውም መሄድ በቻልሁ!

4. ጒዳዬን በፊቱ አቀርብ ነበር፤አፌንም በሙግት እሞላው ነበር።

5. የሚመልስልኝ ቃል ምን እንደሆነ ባወቅሁ ነበር፤የሚለኝንም ባስተዋልሁ ነበር።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 23