ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 22:8-20 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

8. ባለ ርስትና ኀያል፣በእርሱም የምትኖር ክቡር ሰው ብትሆንም፣

9. መበለቶችን ባዶ እጃቸውን ሰደሃል፤የድኻ ዐደጎችንም ክንድ ሰብረሃል።

10. ድንገተኛ አደጋ ያናወጠህ፤ወጥመድም ዙሪያህን የከበበህ ለዚህ ነው።

11. እንዳታይ ጨለማ የሆነብህ፣ጐርፍም ያጥለቀለቀህ ለዚህ ነው።

12. “እግዚአብሔር ከፍ ባለው ሰማይ የሚኖር አይደለምን?በሩቅ ከፍታ ያሉትን ከዋክብት ያያል!

13. ይህም ሆኖ ሳለ እንዲህ አልህ፤ ‘እግዚአብሔር ምን ያውቃል?በእንዲህ ያለ ጨለማ ውስጥስ ይፈርዳልን?

14. በሰማይ ክበብ ላይ ሲራመድ፣እንዳያየን ጥቅጥቅ ያለ ደመና ይሸፍነዋል።’

15. ኀጢአተኞች በሄዱባት፣በጥንቷ መንገድ እንደ ተመላለስህ ትቀራለህን?

16. ጊዜያቸው ሳይደርስ ተነጠቁ፤መሠረታቸውም በጐርፍ ተወሰደ።

17. እግዚአብሔርንም ‘አትድረስብን!ሁሉን የሚችል አምላክም ምን ያደርግልናል?’ አሉ።

18. ቤታቸውን በመልካም ነገር የሞላው ግን እርሱ ነው፤ስለዚህ ከኀጢአተኞች ምድር እርቃለሁ።

19. “ጻድቃንም የእነዚያን ጥፋት አይተው ይደሰታሉ፤ንጹሓንም እንዲህ ብለው ያፌዙባቸዋል፤

20. በእርግጥ ጠላቶቻችን ጠፍተዋል፤ሀብታቸውም በእሳት ተበልቶአል።’

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 22