ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 19:1-10 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ኢዮብም እንዲህ ሲል መለሰ፤

2. “ነፍሴን የምታስጨንቋት፣በቃልስ የምትደቍሱኝ እስከ መቼ ነው?

3. እነሆ፤ ዐሥር ጊዜ ዘለፋችሁኝ፤ያለ ዕፍረትም በደላችሁኝ።

4. በእውነት ተሳስቼ ከሆነ፣ስሕተቱ የራሴ ጒዳይ ነው።

5. ነገር ግን ራሳችሁን በእኔ ላይ ከፍ ብታደርጉ፣መዋረዴንም እኔን ለመሞገት ብትጠቀሙበት፣

6. እግዚአብሔር እንደ በደለኝ፣በመረቡም እንደ ከበበኝ ዕወቁ።

7. “ ‘ተበደልሁ’ ብዬ ብጮኽ ማንም አይመልስልኝም፤ድምፄን ከፍ አድርጌ ባሰማም፣ ፍትሕ አላገኝም።

8. እንዳላልፍ መንገዴን ዘግቶአል፤መሄጃዬንም በጨለማ ጋርዶአል።

9. ክብሬን ገፍፎኛል፤ዘውዴንም ከራሴ ላይ ወስዶአል።

10. እስክወገድ ድረስ በሁሉ አቅጣጫ አፈራርሶኛል፤ተስፋዬንም እንደ ዛፍ ነቅሎታል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 19