ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 18:1-7 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ሹሐዊው በልዳዶስ እንዲህ ሲል መለሰ፤

2. “ይህን ንግግር የምትጨርሰው መቼ ነው?እስኪ ልብ ግዛ፤ ከዚያ በኋላ እንነጋገራለን።

3. ለምን እንደ ከብት መንጋ እንቈጠራለን?እንደ ደንቈሮስ ለምን ታየናለህ?

4. አንተ በቍጣ የነደድህ እንደሆነ፣ምድር ባዶዋን ትቀራለች?ወይስ ዐለት ከሥፍራው ተነቅሎ ይወሰዳል?

5. “የክፉዎች መብራት ይጠፋል፤የእሳቱም ነበልባል ድርግም ይላል።

6. የድንኳኑ ብርሃን ይጨልማል፤መብራቱም በላዩ ይጠፋል፤

7. የርምጃው ብርታት ይደክማል፤የገዛ ዕቅዱም ይጥለዋል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 18