ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 16:2-6 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

2. “ይህን የሚመስል ብዙ ነገር ሰምቻለሁ፤እናንተ ሁላችሁ የምታስጨንቁ አጽናኞች ናችሁ።

3. ይህ ከንቱ ንግግር አያልቅምን?ትለፈልፍ ዘንድ የሚገፋፋህ ምንድን ነው?

4. እናንተ በእኔ ስፍራ ብትሆኑ ኖሮ፣እኔም እንደ እናንተ መናገር እችል ነበር፤ቃላት አሳክቼ በመናገር፣በእናንተ ላይ ራሴን መነቅነቅ በቻልሁ ነበር።

5. ይልቁንም አንደበቴ ባበረታታችሁ፣የከንፈሬም ማጽናናት ባሳረፋችሁ ነበር።

6. “ብናገር ሕመሜ አይሻለኝም፤ዝም ብልም አይተወኝም።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 16