1. “ይህን ሁሉ ዐይኔ አይቶአል፤ጆሮዬም ሰምቶ አስተውያለሁ፤
2. እናንተ የምታውቁትን፣ እኔም ዐውቃለሁ፤ከእናንተ የማንስ አይደለሁም።
3. ነገር ግን ሁሉን ከሚችል አምላክ ጋር መነጋገር እፈልጋለሁ፤ከእግዚአብሔርም ጋር መዋቀስ እሻለሁ።
4. እናንተ ግን፣ በሐሰት የምትለብጡ ናቸሁ፤ሁላችሁ የማትረቡ ሐኪሞች ሆናችኋል።
5. ምነው ዝም ብትሉ!ያ ከጥበብ ይቈጠርላችሁ ነበር!
6. እንግዲህ ክርክሬን ስሙ፤የከንፈሬንም አቤቱታ አድምጡ።
7. ለእግዚአብሔር ብላችሁ በክፋት ትናገራላችሁን?ስለ እርሱስ በማታለል ታወራላችሁን?