ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዩኤል 3:16-21 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

16. እግዚአብሔር ከጽዮን ጮኾ ይናገራል፤ከኢየሩሳሌም ያንጐደጒዳል፤ሰማይና ምድርም ይናወጣሉ፤ እግዚአብሔር ግን ለሕዝቡ መሸሸጊያ፣ለእስራኤልም ልጆች መጠጊያ ይሆናል።

17. “ከዚያም እኔ አምላካችሁ እግዚአብሔር፣በቅዱሱ ተራራዬ በጽዮን እንደምኖር ታውቃላችሁ፤ኢየሩሳሌም የተቀደሰች ትሆናለች፤ከእንግዲህም ወዲያ ባዕዳን አይወሯትም።

18. “በዚያ ጊዜ ተራሮች፣ አዲስ የወይን ጠጅ ያንጠባጥባሉ፤ኰረብቶችም ወተት ያፈሳሉ፤በይሁዳ ያሉ ሸለቆዎች ሁሉ ውሃ ያጐርፋሉ፤ ከእግዚአብሔር ቤት ምንጭ ይፈልቃል፤የሰጢምን ሸለቆ ያጠጣል።

19. ግብፅ ባድማ፣ኤዶምም ምድረ በዳ ትሆናለች፤በምድራቸው ንጹሕ ደም በማፍሰስ፣በይሁዳ ሕዝብ ላይ ግፍ ፈጽመዋልና።

20. ይሁዳ ለዘላለም፣ኢየሩሳሌምም ለትውልድ ሁሉ መኖሪያ ትሆናለች፤

21. ደማቸውን እበቀላለሁ፤በደለኛውንም ንጹሕ አላደርግም።” እግዚአብሔር በጽዮን ይኖራል!

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዩኤል 3