ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዩኤል 1:5-12 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

5. እናንት ሰካራሞች፤ ተነሡ፤ አልቅሱ፤እናንት የወይን ጠጅ ጠጪዎች ሁሉ፤ ዋይ በሉ፤ስለ አዲሱ የወይን ጠጅ ዋይ ብላችሁ አልቅሱ፤አፋችሁ ላይ እንዳለ ተነጥቃችኋልና።

6. ኀያልና ቊጥር ስፍር የሌለው ሕዝብ፣ምድሬን ወሮአታልና፤ጥርሱ እንደ አንበሳ ጥርስ፣መንጋጋውም እንደ እንስት አንበሳ መንጋጋ ነው።

7. የወይን ቦታዬን ባድማ አደረገው፤የበለስ ዛፎቼንም ቈራረጠ፤ቅርንጫፎቻቸው ነጭ ሆነው እስኪታዩ ድረስ፣ቅርፊታቸውን ልጦ፣ወዲያ ጣላቸው።

8. የልጅነት እጮኛዋን እንዳጣች ድንግል፣ማቅ ለብሳችሁ አልቅሱ።

9. የእህል ቊርባንና የመጠጥ ቍርባን፣ ከእግዚአብሔር ቤት ተቋርጦአል፤ በእግዚአብሔርም ፊት የሚያገለግሉ፣ካህናት ያለቅሳሉ።

10. ዕርሻዎች ባዶአቸውን ቀርተዋል፤ምድሩም ደርቆአል፤እህሉ ጠፍቶአል፤አዲሱ የወይን ጠጅ አልቆአል፤ዘይቱም ተሟጦአል።

11. እናንት ገበሬዎች፣ ዕዘኑ፤እናንት የወይን ገበሬዎች፣ ዋይ በሉ፤ስለ ገብሱና ስለ ስንዴው አልቅሱ፤የዕርሻው መከር ጠፍቶአልና።

12. ወይኑ ደርቆአል፤የበለስ ዛፉም ጠውልጎአል፤ሮማኑ፣ ተምሩና እንኮዩ፣የዕርሻው ዛፎች ሁሉ ደርቀዋል፤ስለዚህ ደስታ፣ከሰው ልጆች ርቆአል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዩኤል 1