ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዩኤል 1:1-7 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ወደ ባቱኤል ልጅ ወደ ኢዩኤል የመጣው የእግዚአብሔር ቃል ይህ ነው፤

2. እናንት ሽማግሌዎች፣ ይህን ስሙ፤በምድሪቱም የምትኖሩ ሁላችሁ፣ አድምጡ፤በእናንተ ዘመን፣ ሆነ በአባቶቻችሁም ዘመን፣እንዲህ ዐይነት ነገር ሆኖ ያውቃልን?

3. ይህን ለልጆቻችሁ ተናገሩ፤ልጆቻችሁ ለልጆቻቸው ይንገሩ፤ልጆቻቸውም ለሚቀጥለው ትውልድ ይንገሩ።

4. ከአንበጣ መንጋ የተረፈውን፣ትልልቁ አንበጣ በላው፤ከትልልቁ አንበጣ የተረፈውን፣ኵብኵባ በላው፤ከኵብኵባ የተረፈውን፣ሌሎች አንበጦች በሉት።

5. እናንት ሰካራሞች፤ ተነሡ፤ አልቅሱ፤እናንት የወይን ጠጅ ጠጪዎች ሁሉ፤ ዋይ በሉ፤ስለ አዲሱ የወይን ጠጅ ዋይ ብላችሁ አልቅሱ፤አፋችሁ ላይ እንዳለ ተነጥቃችኋልና።

6. ኀያልና ቊጥር ስፍር የሌለው ሕዝብ፣ምድሬን ወሮአታልና፤ጥርሱ እንደ አንበሳ ጥርስ፣መንጋጋውም እንደ እንስት አንበሳ መንጋጋ ነው።

7. የወይን ቦታዬን ባድማ አደረገው፤የበለስ ዛፎቼንም ቈራረጠ፤ቅርንጫፎቻቸው ነጭ ሆነው እስኪታዩ ድረስ፣ቅርፊታቸውን ልጦ፣ወዲያ ጣላቸው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዩኤል 1