ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 8:12-19 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

12. “እነዚህ ሰዎች፣ ‘አድማ’ ብለው የሚጠሩትን፣ማንኛውንም ነገር፣ ‘አድማ’ አትበሉ፤እነርሱ የሚፈሩትን አትፍሩ፤አትሸበሩለትም።

13. ልትቀድሱ የሚገባው የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔርን ብቻ ነው፤ልትፈሩት የሚገባው እርሱን ነው፤ልትንቀጠቀጡለት የሚገባውም እርሱ ነው።

14. እርሱም መቅደስ ይሆናል፤ለሁለቱ የእስራኤል ቤት ግንየሚያደናቅፍ ድንጋይየሚያሰናክልም ዐለት ይሆንባቸዋል፤ለኢየሩሳሌም ሕዝብምወጥመድና አሽክላ ይሆናል።

15. ከእነርሱ ብዙዎች ይሰናከላሉ፤ይወድቃሉ፤ ይሰበራሉ፤ወጥመድ ይገባሉ፤ ይያዛሉም።”

16. ምስክርነቱን አሽገው፤ሕጉንም በደቀ መዛሙርቴ መካከል አትመው።

17. ፊቱን ከያዕቆብ ቤት የሸሸገውን እግዚአብሔርን እጠብቃለሁ፤እርሱንም ተስፋ አደርጋለሁ።

18. እነሆ፤ እኔና እግዚአብሔር የሰጠኝ ልጆች በጽዮን ተራራ ከሚኖረው ከሰራዊት ጌታ ከእግዚአብሔር ለእስራኤል ምልክትና ድንቅ ነን።

19. ሰዎች፣ “የሚያነበንቡትንና የሚያሾካ ሹኩትን ሟርተኞችንና መናፍስት ጠሪዎችን ጠይቁ ቢሏችሁ፣ ሕዝቡ አምላኩን መጠየቅ አይገባውምን? በሕያዋን ምትክ ሙታንን መጠየቅ ለምን አስፈለገ?

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 8