ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 66:8-13 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

8. እንዲህ ያለ ነገር ማን ሰምቶ ያውቃል?እንዲህ ያለ ነገርስ ማን አይቶ ያውቃል?አገር በአንድ ጀምበር ይፈጠራልን?ወይስ ሕዝብ በቅጽበት ይገኛል?ጽዮንን ምጥ ገና ሲጀምራት፣ልጆቿን ወዲያውኑ ትወልዳለች።

9. ሊወለድ የተቃረበውን፣እንዳይወለድ አደርጋለሁን?” ይላል እግዚአብሔር።“በሚገላገሉበት ጊዜስ፣ማሕፀን እዘጋለሁን?” ይላል አምላክሽ።

10. “ወዳጆቿ የሆናችሁ ሁሉ፣ከኢየሩሳሌም ጋር ደስ ይበላችሁ፤ስለ እርሷም ሐሤት አድርጉ፤ለእርሷ ያለቀሳችሁ ሁሉ፣ከእርሷ ጋር እጅግ ደስ ይበላችሁ።

11. ከሚያጽናኑ ጡቶቿ፣ትጠባላችሁ፤ ትረካላችሁም፤እስክትረኩም ትጠጣላችሁ፤በተትረፈረፈ ሀብቷም ትደሰታላችሁ።”

12. እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“እነሆ፤ ሰላምን እንደ ወንዝ ውሃ አፈስላታለሁ፤የመንግሥታትንም ብልጥግና እንደ ጅረት ውሃ አጐርፍላታለሁ፤ትጠባላችሁ፤ በዕቅፏም ትያዛላችሁ፤በጭኖቿም ላይ ትፈነድቃላችሁ።

13. እናት ልጇን እሹሩሩ እንደምትል፣እኔም እናንተን እሹሩሩ እላችኋለሁ፤በኢየሩሳሌምም ትጽናናላችሁ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 66