ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 66:12-15 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

12. እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“እነሆ፤ ሰላምን እንደ ወንዝ ውሃ አፈስላታለሁ፤የመንግሥታትንም ብልጥግና እንደ ጅረት ውሃ አጐርፍላታለሁ፤ትጠባላችሁ፤ በዕቅፏም ትያዛላችሁ፤በጭኖቿም ላይ ትፈነድቃላችሁ።

13. እናት ልጇን እሹሩሩ እንደምትል፣እኔም እናንተን እሹሩሩ እላችኋለሁ፤በኢየሩሳሌምም ትጽናናላችሁ።

14. ይህን ስታዩ፣ ልባችሁ ሐሤት ያደርጋል፤ዐጥንቶቻችሁም እንደ ሣር ይለመልማሉ፤ የእግዚአብሔር እጅ ከባሮቹ ጋር መሆኑ ይታወቃል፤ቊጣው ግን በጠላቶቹ ላይ ይገለጣል።

15. እነሆ፤ እግዚአብሔር በእሳት ነበልባል ይመጣል፤ሠረገሎቹም እንደ ዐውሎ ነፋስ ናቸው፤ንዴቱን በቍጣ፣ተግሣጹንም በእሳት ነበልባል ይገልጣል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 66