ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 58:1-6 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. “በኀይል ጩኽ፤ ምንም አታስቀር፤ድምፅህን እንደ መለከት አሰማ፤ለሕዝቤ ዐመፃቸውን፣ለያዕቆብም ቤት ኀጢአታቸውን ተናገር።

2. ዕለት በዕለት ይፈልጉኛል፤መንገዴን ለማወቅ የሚጓጉ ይመስላሉ፤ትክክለኛውን ነገር እንደሚያደርግ፣የአምላኩንም ትእዛዝ እንዳልተወ ሕዝብ ሁሉ፣ተገቢ የሆነ ፍትሕ ይለምኑኛል፤እግዚአብሔር ወደ እነርሱ እንዲቀርብ የሚወዱም ይመስላሉ።

3. ‘አንተ ካልተቀበልኸው፣ስለ ምን ብለን ጾምን?አንተ ከጒዳይ ካልቈጠርኸው፣ስለ ምን ራሳችንን አዋረድን?’ ይላሉ።“ሆኖም በጾማችሁ ቀን የልባችሁን ታደርጋላችሁ፤ሠራተኞቻችሁንም ትበዘብዛላችሁ።

4. ጾማችሁ በጥልና በክርክር፣በግፍ ጡጫና በመደባደብ ይፈጸማል፤ከእንግዲህ ዛሬ እንደምትጾሙት ጾማችሁ፣ድምፃችሁ ወደ ላይ እንደሚሰማም ተስፋ አታድርጉ።

5. እኔ የመረጥሁት ጾም እንዲህ ዐይነቱን ነውን?ሰውስ ራሱን የሚያዋርደው በእንዲህ ያለው ቀን ብቻ ነውን?እንደ ደንገል ራስን ዝቅ ማድረግ ነውን?ወይስ ማቅ ለብሶ በዐመድ ላይ መንከባለል ነውን?ታዲያ ጾም ብለህ የምትጠራው ይህን ነውን? እግዚአብሔርስ የሚቀበለው እንዲህ ያለውን ቀን ነውን?

6. “እንግዲህ እኔ የመረጥሁት ጾም፣የጭቈናን ሰንሰለት እንድትበጥሱ፣የቀንበርን ገመድ እንድትፈቱ፣የተጨቈኑትን ነጻ እንድታወጡ፣ቀንበርን ሁሉ እንድትሰብሩ አይደለምን?

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 58