ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 56:7-11 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

7. ወደ ተቀደሰው ተራራዬ አመጣቸዋለሁ፤በጸሎት ቤቴም ውስጥ ደስ አሰኛቸዋለሁ።የሚቃጠል መሥዋዕታቸውንና ሌሎች መሥዋዕቶቻቸውን፣በመሠዊያዬ ቢሠዉ እቀበላቸዋለሁ፤ቤቴ፣ ለሕዝቦች ሁሉየጸሎት ቤት ተብሎ ይጠራልና።”

8. የተበተኑትን እስራኤል የሚሰበስብ፣ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ከተሰበሰቡት በተጨማሪ፣ሌሎችን እንደ ገና እሰበስባለሁ።”

9. እናንት የምድር አራዊት ሁሉ ኑ፤እናንት የዱር አራዊት ሁሉ ኑና በጥርሳቸሁ ቦጫጭቁ።

10. የእስራኤል ጠባቂዎች ዕውሮች ናቸው፤ዕውቀት የላቸውም፤ሁሉም ድምፅ የለሽ ውሾች ናቸው፤መጮኽ አይችሉም፤ተጋድመው ያልማሉ፤እንቅልፋሞች ናቸው።

11. እጅግ ሲበዛ ሆዳም ውሾች ናቸው፤ጠገብሁን አያውቁም፤የማያስተውሉ እረኞች ናቸው፤ሁሉም በየራሳቸው መንገድ ሄዱ፤እያንዳንዳቸውም የግል ጥቅማቸውን ፈለጉ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 56