ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 56:1-6 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ፍትሕን ጠብቁ፤መልካሙን አድርጉ፤ማዳኔ በቅርብ ነው፤ጽድቄም ፈጥኖ ይገለጣልና።

2. ሰንበትን ሳያረክስ የሚያከብር፣ክፉን ከማድረግ እጁን የሚሰበስብ፣ የሚገታ፣እነዚህን የሚፈጽም ሰው የተባረከ ነው።”

3. ወደ እግዚአብሔር የተጠጋ መጻተኛ፣“እግዚአብሔር በርግጥ ከሕዝቡ ይለየኛል” አይበል፤ጃንደረባም፣“እኔ ደረቅ ዛፍ ነኝ” አይበል።

4. እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ሰንበቶቼን ለሚያከብሩ ጃንደረቦች፣ደስ የሚያሰኘኝን ለሚመርጡ፣ቃል ኪዳኔን፣ ለሚጠብቁ

5. በቤተ መቅደሴና በቅጥሮቼ ውስጥ፣ከወንዶችና ከሴቶች ልጆች የበለጠ፣መታሰቢያና ስም እሰጣቸዋለሁ፤ለዘላለም፣የማይጠፋ ስም እሰጣቸዋለሁ።

6. እርሱን ለማገልገል፣ራሳቸውን ከእግዚአብሔር ጋር ያቈራኙ መጻተኞች፣ የእግዚአብሔርን ስም በመውደድ፣እርሱንም በማምለክ፣ሰንበትን ሳያረክሱ የሚያከብሩትን ሁሉ፣ቃል ኪዳኔንም የሚጠብቁትን፣

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 56