ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 54:2-9 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

2. “የድንኳንሽን ቦታ አስፊ፤የድንኳንሽን መጋረጃዎች በትልቁ ዘርጊ፤ፈጽሞ አትቈጥቢ፤ገመዶችሽን አርዝሚአቸው፤ካስማዎችሽንም ቀብቅቢ።

3. ወደ ቀኝም ወደ ግራም ትስፋፊያለሽ፤ዘሮችሽ መንግሥታትን ይወርሳሉ፤በባድማ ከተሞቻቸውም ይኖራሉና።

4. “አይዞሽ አትፍሪ፤ ኀፍረት አይገጥምሽም፤ውርደት ስለማይደርስብሽ አትሸማቀቂ፤የወጣትነት ኀፍረትሽን ትረሺዋለሽ፤የመበለትነት ስድብሽንም ከእንግዲህ አታስታውሺውም።

5. ባልሽ ፈጣሪሽ ነውና፤ስሙም የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ነው፤ታዳጊሽ የእስራኤል ቅዱስ ነው፤እርሱም የምድር ሁሉ አምላክ ይባላል።

6. እንደ ተናቀች የልጅነት ሚስት፣ከልብ እንዳዘነችና እንደ ተጠላች ሚስት፣ እግዚአብሔር እንደ ገና ይጠራሻል”ይላል አምላክሽ።

7. “ለጥቂት ጊዜ ተውሁሽ፤ነገር ግን በታላቅ ርኅራኄ መልሼ እሰበስብሻለሁ።

8. ለጥቂት ጊዜ እጅግ ስለ ተቈጣሁ፣ፊቴን ከአንቺ ሰወርሁ፤ነገር ግን በዘላለማዊ ቸርነቴ፣እራራልሻለሁ”ይላል ታዳጊሽ እግዚአብሔር።

9. “ይህ ለእኔ የኖኅ ውሃ ምድርን ዳግመኛ እንዳያጥለቀልቃት እንደማልሁበት፣እንደ ኖኅ ዘመን ነው፤አሁንም አንቺን ዳግም እንዳልቈጣ፣እንዳልገሥጽሽም ምያለሁ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 54