ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 49:10-19 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

10. አይራቡም፤ አይጠሙም፤የምድረ በዳ ትኵሳት ወይም የፀሓይ ቃጠሎ አይጐዳቸውም።የሚራራላቸው ይመራቸዋል፤በውሃ ምንጭ ዳርም ያሰማራቸዋል።

11. ተራሮቼን ሁሉ መንገድ አደርጋለሁ፤ጐዳናዎቼም ከፍ ይላሉ።

12. እነሆ፤ ከሩቅ አገር ይመጣሉ፤አንዳንዶች ከሰሜን ሌሎች ከምዕራብ፣የቀሩት ደግሞ ከሲኒም ይመጣሉ።

13. ሰማያት ሆይ፤ እልል በሉ፤ምድር ሆይ፤ ደስ ይበልሽ፤ተራሮች ሆይ፤ በደስታ ዘምሩ፤ እግዚአብሔር ሕዝቡን ያጽናናል፤ለተቸገሩትም ይራራልና።

14. ጽዮን ግን፣ “እግዚአብሔር ትቶኛል፤ጌታም ረስቶኛል” አለች።

15. “እናት የምታጠባውን ልጇን ልትረሳ ትችላለችን?ለወለደችውስ ልጅ አትራራለትምን?ምናልባት እርሷ ትረሳ ይሆናል፣እኔ ግን እልረሳሽም።

16. እነሆ፤ በእጄ መዳፍ ላይ ቀርጬሻለሁ፤ቅጥሮችሽ ምንጊዜም በፊቴ ናቸው።

17. ወንዶች ልጆችሽ ፈጥነው ይመለሳሉ፤ያፈራረሱሽም ከአንቺ ይሸሻሉ።

18. ዐይንሽን ቀና አድርጊ፤ ዙሪያውንም ተመልከቺ፤ወንዶች ልጆችሽ ሁሉ ተሰብስበው ወደ አንቺ ይመጣሉ።“በሕያውነቴ እምላለሁ፤እነዚህን ሁሉ እንደ ጌጥ ትለብሻቸዋለሽ፤እንደ ሙሽራም ትጐናጸፊያቸዋለሽ” ይላል እግዚአብሔር።

19. “ፈራርሰሽ ባድማ ብትሆኚ፣ምድርሽ ፈጽሞ ቢጠፋ፣ዛሬ ለሕዝብሽ ጠባብ ብትሆኚም እንኳ፣የዋጡሽ ከአንቺ ይርቃሉ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 49