ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 40:7-12 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

7. ሣሩ ይደርቃል፤ አበባውም ይረግፋል፤ የእግዚአብሔር እስትንፋስ ነፍሶበታልና፤ሕዝቡ በርግጥ ሣር ነው።

8. ሣሩ ይደርቃል፤ አበባውም ይረግፋል፤የአምላካችን ቃል ግን ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል።”

9. አንተ ለጽዮን የምሥራችን የምትነግር፤ከፍ ወዳለው ተራራ ውጣ፤አንተ ለኢየሩሳሌም ብሥራት የምትነግር፣ድምፅህን ከፍ አድርገህ ጩኽ።ከፍ አድርገው፤ አትፍራ፤ለይሁዳም ከተሞች፣“እነሆ፤ አምላካችሁ!” በል።

10. እነሆ፤ ልዑል እግዚአብሔር በኀይልይመጣል፤ክንዱ ስለ እርሱ ይገዛል።እነሆ፤ ዋጋው ከእርሱ ጋር ነው፤የሚከፍለውም ብድራት አብሮት አለ።

11. መንጋውን እንደ እረኛ ያሰማራል፤ጠቦቶቹን በክንዱ ይሰበስባል፤በዕቅፉም ይይዛቸዋል፤የሚያጠቡትንም በጥንቃቄ ይመራል።

12. ውሆችን በዕፍኙ የሰፈረ፣ሰማያትን በስንዝሩ የለካ፣የምድርን ዐፈር በመስፈሪያ ሰብስቦ የያዘ፣ተራሮችን በሚዛን፣ኰረብቶችንም በመድሎት የመዘነ ማነው?

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 40