ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 40:11-17 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

11. መንጋውን እንደ እረኛ ያሰማራል፤ጠቦቶቹን በክንዱ ይሰበስባል፤በዕቅፉም ይይዛቸዋል፤የሚያጠቡትንም በጥንቃቄ ይመራል።

12. ውሆችን በዕፍኙ የሰፈረ፣ሰማያትን በስንዝሩ የለካ፣የምድርን ዐፈር በመስፈሪያ ሰብስቦ የያዘ፣ተራሮችን በሚዛን፣ኰረብቶችንም በመድሎት የመዘነ ማነው?

13. የእግዚአብሔርን መንፈስ የተረዳ፣አማካሪውስ ሆኖ ያስተማረው ማነው?

14. ዕውቀት ለማግኘት እግዚአብሔር ማንን አማከረ?ትክክለኛውንስ መንገድ ማን አስተማረው?ዕውቀትን ያስተማረው፣የማስተዋልንም መንገድ ያሳየው ማን ነበር?

15. እነሆ፤ አሕዛብ በገንቦ ውስጥ እንዳለች ጠብታ ናቸው፤በሚዛን ላይ እንዳለ ትቢያ ይቈጠራሉ፤ደሴቶችንም እንደ ደቃቅ ዐፈር ይመዝናቸዋል።

16. ሊባኖስ ለመሠዊያ እሳት አትበቃም፤የእንስሶቿም ቍጥር ለሚቃጠል መሥዋዕት ያንሳል።

17. አሕዛብ ሁሉ በፊቱ እንደ ኢምንት ናቸው፤ከምንም የማይቈጠሩ መና ናቸው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 40