ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 40:1-6 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. አጽናኑ፤ ሕዝቤን አጽናኑ፤ይላል አምላካችሁ።

2. ለኢየሩሳሌም አለዝባችሁ ንገሯት፤ዐውጁላትም፤በባርነት ያገለገለችበት ዘመን አብቅቶአል፤የኀጢአቷም ዋጋ ተከፍሎአል፤ስለ ኀጢአቷ ሁሉ ከእግዚአብሔር እጅሁለት ዕጥፍ ተቀብላለች።

3. የዐዋጅ ነጋሪ ድምፅ እንዲህ ይላል፤“የእግዚአብሔርን መንገድ፣በምድረ በዳ አዘጋጁ፤ለአምላካችን አውራ ጐዳና፣በበረሓ አስተካክሉ።

4. ሸለቆው ሁሉ ከፍ ይላል፤ተራራውና ኰረብታው ሁሉ ዝቅ ይላል፤ወጣ ገባው ምድር ይስተካከላል፤ሰርጓጒጡም ሜዳ ይሆናል።

5. የእግዚአብሔርም ክብር ይገለጣል፤ሰው ሁሉ በአንድነት ያየዋል፤ የእግዚአብሔር አፍ ይህን ተናግሮአልና።”

6. ድምፅም፣ “ጩኽ” አለኝ፤እኔም፣ “ምን ብዬ ልጩኽ?” አልሁ።“ሰው ሁሉ እንደ ሣር ነው፤ክብሩም ሁሉ እንደ ሜዳ አበባ ነው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 40