ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 37:24-31 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

24. በመልእክተኞችህ በኩል፣በጌታ ላይ ብዙ የስድብ ቃል ተናገርህ፤እንዲህም አልህ፤“በሰረገሎቼ ብዛት፣የተራሮችንም ከፍታ፣የሊባኖስንም ጫፍ ወጥቻለሁ፤ረጃጅም ዝግባዎችን፣የተመረጡ ጥዶችን ቈርጫለሁ፤እጅግ ወደራቁት ከፍታዎች፣እጅግ ውብ ወደ ሆኑትም ደኖች ደርሻለሁ፤

25. በባዕድ ምድር ጒድጓዶችን ቈፈርሁ፤ከዚያም ውሃ ጠጣሁ።የግብፅን ምንጮች ሁሉ፣በእግሬ ረግጬ አደረቅሁ።”

26. “ ‘ይህን ቀድሞ እንደ ወሰንሁት፣ጥንትም እንዳቀድሁት፣አልሰማህምን?አሁን ደግሞ እንዲፈጸም አደረግሁት፤አንተም የተመሸጉትን ከተሞች የድንጋይክምር አደረግሃቸው።

27. የሕዝቦቻቸው ኀይል ተሟጦአል፤ደንግጠዋል፤ ተዋርደዋልም፤በሜዳ እንዳሉ ዕፀዋት፣እንደ ለጋ ቡቃያ፣በሰገነት ላይ እንደ በቀለ ሣር፣በእንጭጩ ዋግ እንደ መታው ሆነዋል።

28. “ ‘እኔ ግን የት እንዳለህ፣መምጣት መሄድህ ምን ጊዜ እንደሆነ፣በእኔም ላይ እንዴት በቍጣ እንደም ትነሣሣ ዐውቃለሁ።

29. በእኔ ላይ በቍጣ ስለ ተነሣሣህ፣እብሪትህም ወደ ጆሮዬ ስለ ደረሰ፣በአፍንጫህ ስናጌን፣በአፍህ ልጓሜን አገባለሁ፤በመጣህበትም መንገድ እንድትመለስአደርግሃለሁ።’

30. “ሕዝቅያስ ሆይ፤ ይህ ምልክት ይሆንልሃል፤“በዚህ ዓመት የገቦውን፣በሚቀጥለው ዓመት ከገቦው የበቀለውን ትበላላችሁ፤በሦስተኛው ዓመት ግን ትዘራላችሁ፤ ታጭዳላችሁ፤ወይን ትተክላላችሁ፤ ፍሬውንም ትበላላችሁ።

31. እንደ ገናም የይሁዳ ቤት ቅሬታ፣ሥሩን ወደ ታች ይሰዳል፤ ከላይም ፍሬ ያፈራል፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 37