ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 37:19-25 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

19. አማልክታቸውን ወደ እሳት ጥለዋል፤ በሰው እጅ የተቀረጹ የድንጋይና የዕንጨት ምስሎች እንጂ አማልክት አልነበሩምና።

20. አሁንም፣ እግዚአብሔር አምላካችን ሆይ፤ የምድር መንግሥታት ሁሉ አንተ እግዚአብሔር ብቻ አምላክ እንደሆንህ ያውቁ ዘንድ፣ አቤቱ ከእጁ አድነን።”

21. ከዚህ በኋላ የአሞጽ ልጅ ኢሳይያስ እንዲህ የሚል መልእክት ወደ ሕዝቅያስ ላከ፤ “የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ስለ አሦር ንጉሥ፣ ስለ ሰናክሬም ወደ እኔ ጸልየሃልና፣

22. እግዚአብሔር በእርሱ ላይ የተናገረው ቃል ይህ ነው፤“ ‘ድንግሊቱ የጽዮን ልጅ፣ንቃሃለች፣ አፊዛብሃለች፤የኢየሩሳሌም ልጅ፣አንተ ስትሸሽ ራሷን ነቅንቃብሃለች።

23. የሰደብኸውና ያቃለልኸው ማንን ነው?ድምፅህንስ ከፍ ከፍ ያደረግኸው፣ዐይንህን በትዕቢት ያነሣኸው በማን ላይ ነው?በእስራኤል ቅዱስ ላይ ነው እኮ!

24. በመልእክተኞችህ በኩል፣በጌታ ላይ ብዙ የስድብ ቃል ተናገርህ፤እንዲህም አልህ፤“በሰረገሎቼ ብዛት፣የተራሮችንም ከፍታ፣የሊባኖስንም ጫፍ ወጥቻለሁ፤ረጃጅም ዝግባዎችን፣የተመረጡ ጥዶችን ቈርጫለሁ፤እጅግ ወደራቁት ከፍታዎች፣እጅግ ውብ ወደ ሆኑትም ደኖች ደርሻለሁ፤

25. በባዕድ ምድር ጒድጓዶችን ቈፈርሁ፤ከዚያም ውሃ ጠጣሁ።የግብፅን ምንጮች ሁሉ፣በእግሬ ረግጬ አደረቅሁ።”

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 37