ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 24:5-12 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

5. ምድር በሕዝቧ ትረክሳለች፤ሕግን ጥሰዋል፤ሥርዐትን ተላልፈዋል፤ዘላለማዊውንም ኪዳን አፍርሰዋል።

6. ስለዚህ ርግማን ምድርን ትበላለች፤ሕዝቦቿም ስለ በደላቸው ይቀጣሉ፤ስለዚህ የምድር ነዋሪዎች ተቃጥለዋል፤በጣም ጥቂት የሆኑት ቀርተዋል።

7. አዲሱ የወይን ጠጅ አለቀ፤ የወይኑም ተክል ደረቀ፤ደስተኞችም ሁሉ አቃሰቱ።

8. የከበሮ ደስታ ጸጥ አለ፤የጨፋሪዎች ጩኸት አበቃ፤ደስ የሚያሰኘውም በገና እረጭ አለ።

9. ከእንግዲህ እየዘፈኑ የወይን ጠጅ አይጠጡም፤መጠጡም ለሚጠጡት ይመራል።

10. የፈራረሰችው ከተማ ባድማ ሆነች፤የየቤቱም መግቢያ ተዘጋ።

11. በየአደባባዩ የወይን ጠጅ ያለህ እያሉ ይጮኻሉ፤ደስታው ሁሉ ወደ ሐዘን ይለወጣል፤ሐሤቱም ሁሉ ከምድር ገጽ ጠፍቶአል።

12. ከተማዪቱ ፈጽማ ፈርሳለች፤በሮቿም ደቀው ወድቀዋል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 24