ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 21:1-6 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. በባሕሩ ዳር ባለው ምድረ በዳ ላይ የተነገረ ንግር፤ዐውሎ ነፋስ ከደቡብ እየጠራረገ እንደሚመጣ፣ወራሪ ከአሸባሪ ምድር፣ከምድረ በዳ ይመጣል።

2. የሚያስጨንቅ ራእይ አየሁ፤ከሓዲ አሳልፎ ይሰጣል፤ ዘራፊ ይዘርፋል።ኤላም ሆይ፤ ተነሺ ሜዶን ሆይ፤ ክበቢእርሷ ያደረሰችውን ሥቃይ ሁሉ አስቀራለሁ።

3. ወገቤ በዚህ ሥቃይ ተሞላ፤በምጥ ላይ እንዳለች ሴት ጭንቅ ያዘኝ፤በሰማሁት ነገር ተንገዳገድሁ፤ባየሁትም ነገር ተሸበርሁ።

4. ልቤ ተናወጠ፤ፍርሀት አንቀጠቀጠኝ፤የጓጓሁለት ውጋጋን፣ታላቅ ፍርሀት አሳደረብኝ።

5. ማእዱን አሰናዱ፤ምንጣፉን አነጠፉ፤በሉ፤ ጠጡ!እናንት ሹማምት ተነሡ፤ጋሻውን በዘይት ወልውሉ!

6. ጌታ እንዲህ አለኝ፤“ሂድ፤ ጠባቂ አቁም፤ያየውንም ይናገር፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 21